የታላቁ ዐውደ ዓመት በዓል ምንባባትና መዝሙራት።

መስከረም አንድ ቀን፡ በርእስ ዓውደ ዓመት፥
በድንግል ማርያም፡ በእናቲቱ ልደት፥
በኢየሱስ ክርስቶስ፡ ባምላክ ልጇም ትስብእት፥
የተወረሰውን ዓመተ ምሕረት፥
በአዳምና ሔዋን፥ የዓለሙን ፍጥረት፥
በቅዱሱ ኪዳን፡ የኢትዮጵያን ነጻነት፥
የተላበሱባት፡ በእግዚአብሔርዋ መንግሥት፥
የኢትዮጵያ ሰዎች፥ ደግሞም ኢትዮጵያዊያት፥
ባሉበት ቦታና በኑሮአቸው ዓይነት፥
በግል፥ በቤተሰብ፥ በኅብረተሰብነት፥
ቤተ ክርስቲያና ቸው፡ መካነ ኪዳናት፥
በቅዱሱ መንፈስ፡ በተሰበሰቡበት፥
የመስቀል ማኅተም፡ ኾኗቸው አብነት፥
በ፬ቱ ማዕዘናት በሚፈጸም ሥረዓት፥
በታላቁ በዓል፡ ግጻዌው ወጥቶለት፥
ይኽው ያቅርቡበት፡ የምሥጋናን መሥዋዕት።

መልእክቱን በሙሉ ለመመልከት፡ እንደሚከትለው ይቀጥሉ!...