ቍጥር ፫/፳፻፮ ዓ. ም. ቃለ-ዐዋድ።

ቍጥር ፫/፳፻፮ ዓ. ም. ቃለ-ዐዋድ።

ቃለ ዐዋድ!
እምኢትዮጵያ፡ ዘመንግሥተ እግዚአብሔር።

የአዋጅ ቃል!
ከኢትዮጵያ፡ የእግዚአብሔር መንግሥት።

ስለግእዝ ምንነትና ማንነት።

ኪዳናውያንና ኪዳናውያት የቅዱስ ኪዳኗ ኢትዮጵያ ልጆች! ስለግእዝ ምንነትና ማንነት፡ በሚበቃ አውቃችኋል። ከዚህ እውቀታችሁ የተነሣ፡ በሰብኣዊው ተፈጥሮአችን፡ የዘር ግንዳችን የኾኑት፡ አዳም እና ሔዋን፡ ከፈጣሪያቸውና ከአምላካቸው ከእግዚአብሔር ያገኙትና እርሱ፡ ከእነርሱ፥ እነርሱም፡ ከእርሱ ጋር፥ እርስ በእርሳቸውም ይነጋገሩበት የነበረው: የመጀመሪያው የሰው ልጆች ቋንቋ፡ ግእዝ መኾኑን ተገንዝባችኋል።

ከዚህ ግንዛቤያችሁም የተነሣ፡ በፍጥረት የልደት ዘመን፡ "ወአሐዱ ነገሩ፡ ለኵሉ ዓለም፤ ወአሐዱ ቃሉ።" ማለትም፡ "የሰው ኹሉ ቋንቋው አንድ፥ አነጋገሩም፡ አንድ ነበር።" ተብሎ፡ በቅዱሳት መጻሕፍት ተመዝግቦ የሚዘከረው፡ ያ አንድ ቋንቋ፥ ያ አንድ ንግግር፡ ግእዝ መኾኑን፡ በእምነት ተቀብላችኋል።