ቍጥር ፱/፳፻፯ ዓ.ም. ቃለ-ዐዋድ

ቍጥር ፱/፳፻፮ ዓ. ም. ቃለ-ዐዋድ።

ቃለ ዐዋድ!
እምኢትዮጵያ፡ ዘመንግሥተ እግዚአብሔር።

የአዋጅ ቃል!
ከኢትዮጵያ፡ የእግዚአብሔር መንግሥት።

ስለእግዚአብሔር እም ማንነትና ምንነት ዝክረ ነገር።

ከሰባቱ ቅዱሳት ኪዳናት መካከል፡ የመጀመሪያዎቹ ሦስቱ እና ሰባተኛው የኾነው፡ ኪዳነ ምሕረቱ ሳይጨመር፡ በተለይ፡ በመካከለኛው፡ በኪዳነ ኦሪት ዘሥጋ የተጠቃለሉት፥ "ኪዳነ አብርሃም፥ ኪዳነ ሙሴ እና ኪዳነ ዳዊት" የተባሉት፡ የኋለኞቹ ሦስቱ፡ ለእስራኤል ልጆች የተሰጡ መኾናቸው፥ እነርሱ፡ የእስራኤል ልጆች ግን፡ እነዚህኑ፡ ሦስቱን ኪዳናት፡ አክብረው ሊፈጽሟቸው ባለመቻላቸው፡ ወደእናንተ፡ ወደኢትዮጵያ ልጆቼ ተመልሰው መጥተውና በእናንተ ዘንድ፡ በአደራ ተጠብቀው መኖራቸው፥ እናንተም፡ በትክክለኛው የእውነትና የመንፈስ ቅዱስ አምልኮ ሥርዓታችሁ፡ በምግባር ላይ ዐውላችሁ፡ ስትገለገሉባቸው መቆየታችሁ፡ በኹሉ ዘንድ የታወቀ እውነታ ነው።