የኢትዮጵያውያንና የኢትዮጵያውያት፡ የቃል ኪዳን ጸሎት።

የኢትዮጵያ፡ የቃል ኪዳን ጸሎት።

እኛ፡ የኢትዮጵያ ልጆች፦

እግዚአብሔር፡ ለሰው ልጆች፣ ለወንዶቹም፥ ለሴቶቹም፣ የሰጣቸውን ቃል ኪዳናት፡ ጠብቆ በኖረው፡ በቅዱሱ ኪዳን ኢትዮጵያዊነታችን እናምናለን።

አምላካችን፡ ይህን የኢትዮጵያዊ እና የኢትዮጵያዊት ሕያው ሰውነት፡ በመጀመሪያው የፍጥረት ዘመን፡ በአዳምና ሔዋን ሥርዓተ ጋብቻ፡ በኪዳነ ልቦና መሠረተው፤

ከዚያም፡ በኖኅ ቀስተ ደመና፥ በመልከ ጼዴቅ ቍርባን እና በአብርሃም ግርዛት፡ ገንብቶ አሳደገው፤

በመካከለኛውም የሕግ ዘመን፡ በሙሴ ጽላትና በዳዊት ዙፋን አዋቅሮ፥ የኢትዮጵያዊቷን ንግሥት፡ የማክዳንና የእስራኤላዊዉን ንጉሥ፡ የሰሎሞንን የዘር ሓረጎች በማዋሓድ፡ በኪዳነ ኦሪት አከናወነው፤