ግብረ-ሐዋርያት

ቍጥር ፲፬/፳፻፮ ዓ. ም. ቃለ-ዐዋድ።

ቃለ ዐዋድ!
እምኢትዮጵያ፡ ዘመንግሥተ እግዚአብሔር።

የአዋጅ ቃል!
ከኢትዮጵያ፡ የእግዚአብሔር መንግሥት።

ኢትዮጵያ የእግዚአብሔር መንግሥትን የሚያገለግሉ፡ ኪዳናውያን ኢትዮጵያውያንና ኪዳናውያት ኢትዮጵያውያት ብቻ ሳይኾን፡ እየራሳቸውን፡ ለቅዱሱ ኪዳን ኢትዮጵያዊነት ተዋሕዶ ሃይማኖት ያበቁ፡ እልፍ አእላፋት፡ ሰብኣውያንና ሰብኣውያት ቅዱሳትና ቅዱሳን፡ በመላው ዓለም መኖራቸውን በተመለከተ።