ቃና ዘገሊላ

ሥርዓተ-ተክሊል፡ ዘቅድስት፥ ወዘሓኪም። Sacrament of Matrimony for Qdst and Zehakim.

ይድረስ፦ ለተወደዳችሁ፡ የክህነት ባልደረቦቼ፡ ኪዳናውያት እኅቶቼና ኪዳናውያን ወንድሞቼ!

በእግዚአብሔራዊው ሰላማችን ኢየሱስ መሲሕ የጾሙ መታሰብያ ሓሤት ተመልተን፡ ኹላችንም፡ በእያለንበት፡ ከነቤተሰቦቻችን፡ በመልካሙ ሕይወታችን እንደምንገኝ፣ ለዚህ ቸርነቱም፡ ፈጣሪያችንን፡ ከነእናቱ፡ ያለማቋረጥ እንደምናመሰግን አምናለሁ።

ይህን እ-ጦማር የጻፍሁላችሁ፡ በዚሁ፡ በጾሙ መታሰብያ ጊዜ፡ በኢትዮጵያ፡ የእግዚአብሔር መንግሥት፡ አንድ እንግዳ ተአምር ደርሶ ስለታየ፡ የእርሱን፡ የምሥራች ዜና ላሰማችሁ ብዬ ነው፤ እርሱም፡ እነሆ፦