ጾመ-ኢትዮጵያ

በየካቲት ወር፥ ፳፻፰ ዓ.ም. ዓመታዊው፡ የኪዳነ-ምሕረት በዓላችንና የጾመ ኢትዮጵያ ምሕላችን ማብቂያ፡ ዐብረው በዋሉበት፡ ቅድስትና የተለየች፥ የተመረጠችና የተገለጠች ዕለት በኾነችው፡ ኪዳናዊት፡ የካቲት ፲፮ ቀን የተከሠተ፡ ተኣምራዊ፡ የሥነ-ፍጥረት ትንግርት።

ዮም ፍሥሓ ኮነ!
በእንተ ኢትዮጵያ፡ እግዚአብሔር-እም፡ ድንግል ማርያም፣
ዘታበጽሕ እደዊሃ ኀበ እግዚአብሔርናሃ፡ እንበይነ ፍጥረተ-ዓለም፥
ወበእንተ ኢየሱስ መሲሕ ኢትዮጵያዊ፡ ዳግማይ አዳም፣
ውእቱ አንበሳ፡ እምነገደ ይሁዳ፡ ዘሞኦ ለአርዌ ነዓዊ ዘገዳም፣
እሉ እሙንቱ፡ ዘጸገዉነ ኪዳነ ምሕረት ዘሰብዓቱ ማኅተም።

ዛሬ፡ ደስታ ኾነ!
ስለፍጥረተ-ዓለሙ ድኅነት፡ ትስብእታዊ እጆቿን፡
ወደመለኮታዊው እግዚአብሔርነቷ በዘረጋችው
በኢትዮጵያ፡ እግዚአብሔር-እም፡ ድንግል ማርያምና፣
ነጣቂው የዱር አውሬ የኾነውን ሰይጣንን ባሸነፈው፡
በዳግማዊው አዳም፡ በኢትዮጵያዊው ኢየሱስ መሲሕ ምክንያት፣
እርሱም፡ ከይሁዳ ነገድ የተገኘው፡ ድል አድራጊው አንበሳ ነው!
እኒሁ፡ እናትና ልጅ፡ ባለሰባት ማኅተም የምሕረት ኪዳንን፡
የሰጡንና ያስገኙልን ናቸው።