ቍጥር ፩/፳፻፭ ዓ. ም. የአዋጅ ቃል

ቍጥር ፩/፳፻፭ ዓ. ም. የአዋጅ ቃል

ቃለ ዐዋድ!
እምኢትዮጵያ፡ ዘመንግሥተ እግዚአብሔር።

የአዋጅ ቃል!
ከኢትዮጵያ፡ የእግዚአብሔር መንግሥት።

ለዓለሙ ሰዎች፡ ለችግራቸው ኹሉ፡ የመጨረሻው መልስና መደምደሚያው መፍትሔ ኾና ቀርባ ያለችው፡ ኢትዮጵያ፡ የእግዚአብሔር መንግሥት ብቻ መኾኗን በተመለከተ።

ዓለም ከተፈጠረበት ጊዜ ጀምሮ እስከዛሬ፡ የሰው ልጆች ምድራዊ ኑሮ፡ የምኞትና የስስት፥ የሲቃና የመቃተት፥ የሥቃይና የመከራ፥ የትንንቅና የዕልቂት እሳትና ማዕበል ያልተለየው፡ የቃጠሎና የድምሳሴ ሰለባ ኾኖ ቆይቷል። ይህም የኾነው፡ በሃይማኖቱና በፍልስፍናው፥ በዘር ማንነትና በቀለም ልዩነት፥ በማኅበራዊው ኑሮና በአገዛዙ ኹኔታ፥ በሥነ ብዕሉ፡ የገንዘብና የሀብት ድልድል፥ እንዲሁም፡ በትምህርት አሰጣጡና በሙያው አሰላለፍ ረገድ ያለው አስተሳሰብና አመራር፡ በማናቸውም መልኩና ይዘቱ፡ ከመሠረቱ፡ ከእግዚአብሔራዊው ሥርዓት፡ ፈጽሞ የተለየ፥ የተዛባና የተቃወሰ ከመኾኑ የተነሣ ነው።