ታኅሣሥ ፲፮ ቀን፥ ፳፻፰ ዓ.ም. (26 December 2015)

ቍጥር ፲/፳፻፮ ዓ. ም. ቃለ-ዐዋድ።

ቃለ ዐዋድ!
እምኢትዮጵያ፡ ዘመንግሥተ እግዚአብሔር።

የአዋጅ ቃል!
ከኢትዮጵያ፡ የእግዚአብሔር መንግሥት።

ሰብኣውያን የዓለም መንግሥታት፡ ዓለማዊ፥ ወይም፡ ሥጋዊ (Secularism) የሚለውን ፍልስፍናቸውን በተመለከተ።

"መለኮታዊ ምዕዳን" - ምዕዳን = ተግሣፅና ማስጠንቀቂያ የተመላበት ትምህርታዊ ምክር ነው።

በሰው ልጆች ህልውና ውስጥ፡ እስከዛሬ ባለፈው፥ አኹን ባለውና ወደፊትም እየተከታተለ በሚደርሰው የዘመን ኺደት፡ ግፍ የተመላበት፡ የክፋትና የኃጢኣት፥ ይህን ዓይነቱም ተመሳሳይ ድርጊት መፈጸሙ፥ ኹኔታውም ከዕለት ወደዕለት እየተባባሰ መቀጠሉ፡ ለምን እንደኾነ ልታውቁት የሚገባ እውነታ ነው።