ተደጋጋሚ ጥያቄዎች - Frequently Asked Question

ኢትዮጵያ የእግዚአብሔር መንግሥት አገልግሎት፡ ከመላው ዓለም፡ ቁም-ነገር ያዘሉ በርካታ ጥያቄዎች ተቀብላ ማስተናገድ ከጀመረች፡ እነኾ በርካታ ዓመታት አስቆጥራለች። ለዕድምተኞቻችን፥ ለተከታታዮቻችን፥ ለአገርና ወገን፡ እንዲኹም፡ ለወደፊት ቋሚ ቅርስ እንደሚኾን በማመን፡ የምታስተናግዳቸው እነዚኽ ጥያቄዎች፡ ተገቢ መኾናቸው ቢታመንም፡ አንዳንዶቹ ጥያቄዎች፡ ምናልባት፡ ኹሉም፥ አለዚያ፡ አብዛኛዎቹ፡ ቀደም ብለው ቀርበውልን መልስ በሰጠንባቸው፦

፩ኛ፡ ንቡረ-እድ ኤርምያስ ከበደ ወልደ-ኢየሱስ ባዘጋጇቸውና ዝርዝራቸው፡ በኅዋ-ሰሌዳችን ላይ በሠፈሩት መጻሕፍቶቻችን ውስጥ ተጠቃልለው ሊገኙ ስለሚችሉ፥

ወደ ተደጋጋሚ ጥያቄዎች መመለሻ / Back to Frequently Asked Question

ከእርሱ በላይ ምንም ነገር የሌለ፤ ነገር ግን ኹሉን ነገር ያስገኘ፤ ወደርና ምሳሌ የሌለው፤ ፍጡር አሰቦ ሊደርስበት የማይችል፤ አንድ ረቂቅ ምሥጢራዊ ማዕከል፤ ምንጭና ኃይል ያለው የህልውና ባሕርይ ነው። ይህን የሚታየውንና የማይታየውን ግዙፉንና ረቂቁን፤ የሚንቀሳቀሰውንና የማይንቀሳቀሰውን፤ ሕያውንና ምውቱን ፍጥረት ኹሉ ከራሱ አስቦ የፈጠረ፤ በራሱ አግዝፎ የሠራና ለራሱ አዘጋጅቶ ያቀረበ፤ እርሱ ስለኾነ፤ “ፈጣሪ” ይባላል።

፩ኛ. በግዕዝ፡ “እግዚአ - ብሔር” ሲል፤ “የአገሪቱ፤ የሕዝቡና የመንግሥቱ ፈጣሪና አምላክ፤ ካህንና ንጉሥ” ማለት ነው።

፪ኛ. እግዚአብሔር የአንድነቱ ስም ሲኾን፤ “እግዚእ፡- አብ፡- ሔር” የሚለው ደግሞ የሦስትነቱን ስም ያመለክታል። ይኻውም ፍጥረቱን የፈጠረው ጌታ ወልድ፤ ከአባቱ፤ ከአብና ከሕይወቱ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ያለውን፤ የአንድነትና የሦስትነት ምሥጢር በማሳየቱ ይታወቃል።

ወደ ተደጋጋሚ ጥያቄዎች መመለሻ / Back to Frequently Asked Question

ኢትዮጵያ፡ የእግዚአብሔር መንግሥት፡ በኅዋ ሰሌዳዎቿና መድረኮቿ፡ በሌሎቹም፡ የመገናኛ መስመሮቿ አማካይነት፡ ለአንባብያን ባቀረበቻቸው፡ "ኢትዮጵያዊው፡ በማንነቱ ፍለጋ!"፥ "ኢትዮጵያ፡ የዓለሙ መፋረጃ!"፥ "ኢትዮጵያ እና ኢትዮጵያዊነት"፥ "አዳምና ሔዋን በኢትዮጵያ!"፥ እንዲሁም፡ “ምሥራች! ከእናት ኢትዮጵያ! ለኢትዮጵያ ልጆች፤ ስለኢትዮጵያዊነት"፥ ደግሞም፡ "Ethiopia: The Classic Case"፥ በተባሉት መጻሕፍቷ ውስጥ፡ ስለዚህ፡ ታላቅ ርእሰ ነገር፡ ዝርዝር ሓተታ፡ በሚበቃ ተሰጥቶበታል። እዚህም ላይ፡ ከዚያ መጽሓፋዊ ማብራርያ የተውጣጣ፡ የተጨመቀ አጠቃላይ መግለጫ እንደሚከተለው ቀርቧል።

ረዥም ዕድሜ ባለውና ሕያው በኾነው፡ በኢትዮጵያ ትውፊት፡ ህልውናን አግኝተው፥ እውን ኾነውና በሰውነት ጎልተው የሚታዩ፥ በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ፡ በክብር ተመዝግበው የሚነበቡ፥ እግዚአብሔር አምላክ፡ ከፍጥረት መጀመሪያ አንሥቶ፡ ከሰው ልጆች ጋር የተካየዳቸው፡ ሰባት ኪዳናት ይገኛሉ።

ወደ ተደጋጋሚ ጥያቄዎች መመለሻ / Back to Frequently Asked Question

“ኢትዮጵያዊነት” ከሚለው ቃል ጋር፡ የጥሬ ዘርና የምሥጢር፥ የዘይቤና የትርጉም ተዛምዶ ያላቸው፡ በዓለም ሕዝቦችና ቋንቋዎች ዘንድ የታወቁ፡ አንዳንድ ይፋ ቃላት አሉ። ከእነዚህ መካከል የሚከተሉት ተጠቅሰዋል፦

፩ኛ. “ኢትዮጵያ” ለማለት፡ “ጦብያ” የሚለው ትውፊታዊ፥ ምጽሓፋዊና ሕዝባዊ ቃል፤

፪ኛ. ጥንታውያን የዓለም ፈላስፎችና ደራስያን፡ የኢትዮጵያን፡ ምድራዊት ገነትነትና የኢትዮጵያውያንን መልአካዊ አኗኗር፡ በመንፈስ በማየትና በዜና በመስማት፡ የኢትዮጵያን፡  ማንነትና የኢትዮጵያዊነትን ምንነት፡ በየጽሑፋቸው ለመግለጽ ይጠቀሙበት የነበረው፥ ይህን የመሰለውን ሕይወት፡ በምድር ላይ ለመፍጠርና ለማግኘት ይቻላል በሚል እምነት፡ የሰው ልጅ፡ ዛሬም እየተጠቀመበት የቀጠለው፡ “ዩቶፒያ” (Utopia) የሚለው የቅርስ ቃል፤

፫ኛ. ጥንት፡ በዛሬይቱ ኢትዮጵያ፡ ምድራዊ ክልል ውስጥ ይኖር የነበረ፡ ዓሣ በላተኛ ሕዝብ፡ ተለይቶ ይጠራበት የነበረው “ኢትዮፓጊ” (Ichthyophagi) የሚለው የስያሜ ቃል፤

ወደ ተደጋጋሚ ጥያቄዎች መመለሻ / Back to Frequently Asked Question

ስለ“ኢትዮጵያ” የሚቀርበው መልእክት፡ ሰው-ሠራሽ ከኾነችውና ስለኾነችው፡ ወይም ዓለማውያን የታሪክ ጸሓፊዎችና ምሁራን፡ እንደዚያች አስመስለው፡ ካቀረቡዋትና ስላቀረቧት፡ ወይም በዛሬው ኹኔታ፡ በገሃድ እንደሚታየው፡ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ፡ በሥጋውያን የሥነ መንግሥት ፈሊጠኞች (Politicians) ከተፈጠረችውና ስለተፈጠረችው፡ “አስመሳይቱ ኢትዮጵያ”፡ አይደለም።

ወደ ተደጋጋሚ ጥያቄዎች መመለሻ / Back to Frequently Asked Question

ምስጋና የሚቀርበው፣ የሚገባውም፡ ለሰው ሳይኾን፡ ለእግዚአብሔር ብቻ ነው። ለሰው፡ በሚያስፈልግበትና ደግሞም፡ አግባብ በሚኾንበት ጊዜ፡ የሚመለስለት አጸፋ፡ ‘እግዚአብሔር ይመስገን! እግዚአብሔር ይስጥልኝ! ዋጋህን፥ ዋጋሽን፥ ዋጋውን፥ ዋጋችሁን፡ እግዚአብሔር ይክፈልልኝ! ይባርክህ! ይባርክሽ! ይባርካችሁ!’ ወይም፡ እንደነገሩ ኹኔታ፡ የሚስሰጠው የማበረታች ቃል፡ ‘ጎሽ! መልካም! በርታ! በርቺ! በርቱ!’ የሚለውን የመሰለ ሊኾን ይገባል።

በዚህ ረገድ፡ መምህራችን፣ ‘እናንተ፡ ያዘዝኋችሁን ኹሉ አድርጋችሁ፡ ‘ምንም ያልሠራን አገልጋዮች ነን፤ ያደረግነውም፡ የሚገባንን ነው፤’ በሉ!’ ሲል፡ የሰጠን መሪ ቃል ይታወሳል። ማቴ. ምዕ. ፮፣ ቁ. ፯-፲፭፣፴-፴፫፤

ለሰው፡ ምስጋና አይገባውም! የሚባለው፡ ስለኹለት ምክንያቶች ነው፤

ወደ ተደጋጋሚ ጥያቄዎች መመለሻ / Back to Frequently Asked Question

''መንግሥት''ማ፡ ግዙፉና ረቂቁ ዓለማት፡ በውስጣቸውም፡ በየወገኑና በየፊናው፡ በሕያውነት ያሉት፡ ፳፪ቱ (ኻያ ኹለቱ)፡ ሥነ-ፍጥረታት፡ ገና፡ የመፈጠር ክብርና ጸጋ፣ ብዕልና ሀብት፣ ዕድልና ጥዋ፡ ሳይደርሳቸውና ሳያገኙ፡ በባሕርይ ሕይወቱና ህልውናው፡ መንፈስ የኾነውና በዚህ አኗኗሩም፡ ''ምሉዕ በኵለሄ''፡ ማለትም፡ ''በኹሉ ለመላው'' አንዱ መለኮት፡ ልክ ለሰው ልጆች በነፍስ ወከፍ እንደተሰጠችውና የእግዚአብሔርን መልክ ነሥታ እንደተፈጠረችው፡ ''እስትንፋስ''፡ ይህችዪቱ መንግሥትም፡ የባሕርይው ማንነት ናት።

ወደ ተደጋጋሚ ጥያቄዎች መመለሻ / Back to Frequently Asked Question

ከዓለሙ ሕዝብ ተለይተን፡ ''ኢትዮጵያውያን''፡ የመባልን፡ አክሊለ-ጸጋንና ልብሰ-ተክህኖን፡ በፈቃዳችን ስለተቀዳጀንና ስስለተጐናጸፍን፥ ዘውዱንና በትረ-ሥልጣኑንም፡ በፈቃዳችን ስለደፋንና ስለጨበጥን፥ የጨዋነት (የኢትዮጵያዊነት)፡ ሃይማኖትንና ምግባር መታወቂያንም፡ ስለያዝንና ስላነገብን ብቻ! ፈተናውና መከራው፥ ሥቃዩና ችግሩ፥ ሰቆቃውና ልቅሶው፡ በእኛ፡ በኢትዮጵያውያንና በኢትዮጵያውያት ዘንድ፡ እንደሚጸናና እንደሚበረታ፡ ከቶውኑ አያጠያይቅም።

ወደ ተደጋጋሚ ጥያቄዎች መመለሻ / Back to Frequently Asked Question

ራሱን፡ “የሰው ልጅ” እያለ የሚጠራው፡ የእግዚአብሔር ልጅ የኾነው፡ ዘለዓለማዊው ካህንና እውነተኛው ንጉሥ፡ ኢየሱስ ክርስቶስ፡ በመጨረሻው የሕይወት ዘመን እስኪገለጥ ድረስ፡ “መልከ ጼዴቅ” እና “ንጉሠ ሳሌም”፡ የልዑል እግዚአብሔር ካህንና የሰላም ንጉሥ፡ በሚል ስያሜ፡ የእርሱ ምሳሌ ኾኖ፡ በምድር ላይ የሚታይ፡ አንድ ደግ ሰው፡ ከኖኀ ዘመን አንሥቶ፡ በሰዎች መካከል፡ በተከታታይ፡ በኢየሩሳሌም፡ እየተሠየመ ይኖር ነበር።

ወደ ተደጋጋሚ ጥያቄዎች መመለሻ / Back to Frequently Asked Question

በኢትዮጵያ ሰፍና የምትኖረው የእግዚአብሔር መንግሥት፡ ሦስት የአገልግሎት አካላዊ ዘርፎች አሏት። እነዚህም፦

፩ኛ. ቤተ ሕዝብ

፪ኛ. ቤተ ክህነት እና

፫ኛ. ቤተ ምልክና ይባላሉ።

ጉዳዩን አግዝፎ ለማስረዳት፡ በሰብአዊው ተፈጥሮ፡ ቋሚ የኾነችው የነፍስ አካል፡ ሥጋዊ አካልና መንፈሳዊ አካል እንዳሏት ኹሉ፡ የእግዚአብሔር በኾነችውም መንግሥት፡ ቤተ ሕዝቡ፡ እንደነፍስ፥  ቤተ ምልክናው እንደሥጋ፥ ቤተ ክህነቱም፡ እንደመንፈስ አካላት ኾነው ይመደባሉ።

ወደ ተደጋጋሚ ጥያቄዎች መመለሻ / Back to Frequently Asked Question

ከእግዚአብሔር፡ በእግዚአብሔር ጣቶች፡ የተጻፈባቸውና ኹለቱን ጽላት የያዘችው፡ለሙሴም የተሰጠችው፡ አሥሩን ቃላት የያዘችው ሰሌዳ ጽላት ይባላል። የእርሷ ማኅደር የኾነው ደግሞ ታቦት ይባላል። የመጀመሪያዎቹ አምስቱ፡ ከሃይማኖታዊ አምልኮ ጋር የተያያዙ ሲኾኑ፤ ነፍስ፡ ሃይማኖቷን የምትመሠርትባቸውና እውነተኛነቷን፡ ለራስዋና ለፈጣሪዋ አረጋግጣ የምታሳይባቸው ባሕርያት ናቸው። የኋለኞቹ አምስቱ ደግሞ ከሃይማኖታዊ ምግባር የተያያዙ ሲኾኑ፤ ነፍስ፡ በሥጋዋ አማካይነት፡ ሃይማኖታዊ ምግባዋን፡ ለሌሎች ፍጡራን አረጋግጣ የምታሳይባቸው የሥራ መግለጫዎች ናቸው።

ወደ ተደጋጋሚ ጥያቄዎች መመለሻ / Back to Frequently Asked Question

አዎን! የተለያዩ ናቸው።

ኹለቱን፡ የብሉዩን ኪዳን ጽላት ተክቶ፡ በአዲሱ ታቦት ውስጥ የተቀመጠው፡ አዲሱ፡ አራት ማዕዘን ነጠላ ጽሌ፡ በላዩ ተቀርጾ የሚታየው ጽሑፍ፡ እንደቀደሙት ጽላት፡ አሥሩን ትእዛዛት የያዘው፡ የእግዚአብሔር ቃል ሳይኾን፡ ያ ቃል፡ በድንግል ማርያም ማኅጸን፡ ሰው መኾኑን ለማሳየት፡ በመኻል፡ የኢየሱስ ክርስቶስ ሥነ ስቅለት ኾኖ፡ በቀኝ፡ የቅድስት ድንግል ማርያም፥ በግራ፡ የወንጌላዊው ዮሓንስ ሥዕሎች፥ ዙሪያውንም፡ የእግዚአብሔር፡ የአምላክነቱ ስሞች ተጽፈውና ተሥለው ነው።

ያ፡ ታቦት የሚገኝበት ቤተ መቅደስ፡ በጌታ ወይም በእመቤታችን ስም እንደኾነ፡ ስማቸው፥ አለዚያ፡ መታሰቢያነቱ፡ ለነቢይ፥ ለሓዋርያ፥ ለጻድቅ፥ ለሰማዕት ወይም ለመልአክ ከኾነ፡ የዚያ ቅዱስ ስም፡ “ዝ ጽላት፡ ዘቅዱስ እከሌ” ተብሎ፡ ከጀርባው ይቀረጽበታል።

ወደ ተደጋጋሚ ጥያቄዎች መመለሻ / Back to Frequently Asked Question

“የመጀመሪያዋ ሰንበት”፡ ከኹለተኛዋና ከዘላለማዊቷ “ሰንበተ ክርስቲያን” በፊት፡ አስቀድማ የነበረች መኾኗን ለመግለጽ፡ “ቀዳሚት ሰንበት” ወይም “ቅዳሜ” የሚለው ስያሜ ያረጋግጣል። እንዲህ አድርጋ፡ ኹለቱን ሰንበታት፡ በየመልካቸውና በየማዕርጋቸው የምታከብረው፡ ኢትዮጵያ ብቻ በመኾኗ፡ በዓለም ላይ ካሉ ሃይማኖቶችና አብያተ ክርስቲያናት መካከል፡ እርሷ ለያዘችው ቀዳሚነት፡ አንዱ ማስረጃ፡ ይህ መኾኑን ማስተዋል ይገባል።

ኋላ፡ እግዚአብሔር፡ ታቦተ ጽዮንን፡ ከእስራኤላውያን እጅ አውጥቶ፡ በባለአደራነት፡ ለእነርሱ፡ ለኢትዮጵያውያን እንድትሰጥ ያደረገው፡ አንዱም፡ በዚሁ፡ በኪዳነ ልቦና ይፈጽሙት በነበረው፡ ንጽሕ አምልኮታቸው ምክንያት መኾኑ፡ ሊታበል ከቶ አይቻልም። ይኽም እውነታ፡ ዓለም በተቀበላቸው፡ ቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ ስማቸው በተመዘገበው፡ በመልከ ጼዴቅ፥ በዮቶርና በንግሥት ሳባ ሃይማኖት፥ አምልኮና ምጋባር ተረጋግጦ ይታወቃል።

(ለተጨማሪ ማብራሪያ ኢትዮጵያ፡ የዓለሙ መፋረጃ! ከገጽ ፸፯ ጀምሮ ይመልከቱ)

ወደ ተደጋጋሚ ጥያቄዎች መመለሻ / Back to Frequently Asked Question

በቅዱሱ ኪዳን ጸንታ የኖረችው፡ ጥንታዊቷ ኢትዮጵያ፡ ቀደም ብላ፡ ከኪዳነ ልቦና ወደኪዳነ ኦሪት ተሸጋግራ ከቆየችበት እምነቷ፡ በምሥጢረ ጥምቀት፡ ለክርስትና እምነት፡ ማለትም፡ ለኪዳነ መንፈስ ቅዱስ የበቃችው፡ ከክርስቶስ ልደት በኃላ፡ አርባ ዓመት ሳይሞላ እንደኾነ ይታወቃል። ይኹን እንጂ፡ ቤተ ክህነቷ፡ “ቤተ ክርስቲያን” ተብላ፡ እንደአዲስ የተቋቋመችው፡ ክርስቶስ በተወለደ፡ በአራተኛው ምዕት ዓመት እንደኾነ የሚያስመስል፡ የሓሰት ይትበሃል፡ በግብፃውያን አማካኝነት ሠርጎ እንዲገባ ተደርጓል። የዚሁ፡ የባዕዳኑ ይትበሃል ጠንቀኛ ውጤቶች የኾኑትን፡ “Coptic” (ኮፕቲክ) እና “Orthodox” (ኦርቶዶክስ) የተባሉትን፡ የግብጽና የግሪክ የሃይማኖት መለያ የኾኑትን ቃላት፡ በተቀጽላነት በመጨመር፡ “የኢትዮጵያ Coptic ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን” ወይም “የኢትዮጵያ Orthodox ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን” የሚለው አጠራር ጸንቶ እንዲቀጥል ተደርጓል።

ወደ ተደጋጋሚ ጥያቄዎች መመለሻ / Back to Frequently Asked Question

የሃይማኖት ወገኖቻችን በኾኑት፡ በባዕዳን አብያተ ክርስቲያናት፡ በተለይም፡ በግብፅ ቤተ ክርስቲያን የተጽዕኖ ኃይል ሠርገው ገብተው፡ መሠረት ከያዙትና እስከዛሬ ድረስ በኢትዮጵያውያን የእምነት ባህል ላይ ሰፍነው ከሚታዩት፡ ረቂቃን ደባዎች መካከል፡ ጥቂቱን፡ እስቲ፡ አልፎ አልፎ፡ ከዚኽ እንደሚከተለው እንመልከት!

፩ኛ. “የአዳምና ሔዋን ልሳን” ተብሎ፡ ለዓለም ቋንቋዎች፡ ሥርና ግንድ ለኾነው ለ“ግዕዝ” ማንነት፡ መታወቂያው የኾነውንና በአሌፋቱ (በፊደሎቹ) ተራ፡ በግልጽ የሚታወቀውን፡ የ“አ(ኧ)በገደ”ን ሥርዓተ ፊደል፡ ግብፃውያን፡ ኾን ብለው፡ መሠረታዊ አቋሙን አፋልሰው፡ ደብዛውን ጭምር ለማጥፋት ሲሉ፡ ሥርዓቱን፡ ወደ“ሀሁ” ለውጠዋል።

ወደ ተደጋጋሚ ጥያቄዎች መመለሻ / Back to Frequently Asked Question

እኛ፡ የቅዱሱ ኪዳን ኢትዮጵያውያን፡ የመጀመሪያው ትንሣኤ ሕይወት ባለዕድሎች ስለኾንን፡ ‘የትንሣኤ ብርሃን ልጆች!’ ነንና፡ ከደስታ በስተቀር፡ ኀዘን የለብንም። በሠርግ፥ ወይም፡ የደስታ በዓሎቻችንን በምናከብርባቸው ጊዜያት ብቻ ሳይኾን፡ ሕያዋን ወገኖቻችን፡ ከመካከላችን፡ በሥጋ ዕረፍት ሲያንቀላፉ፥ ነጭ ልብስን ለብሰን፡ በሓሤት ተመልተን የምንሸኛቸው፡ በዚህ ምክንያት ነው። ጌታ፡ ‘ሙታናቸውን ይቀብሩ ዘንድ፡ ሙታንን ተዉዋቸው!’ ያላቸው፡ ሌሎች፡ “ክርስቲያኖች ነን” ባዮች ግን፡ የሞቱ ወገኖቻቸውን፡ ጥቁር ልብስን ለብሰውና መራራ የኀዘን ልቅሶን በማድረግ ሲቀብሩዋቸው እናያለን።

ወደ ተደጋጋሚ ጥያቄዎች መመለሻ / Back to Frequently Asked Question

እኛ የቅዱሱ ኪዳን ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያት፡ በክርስትና ጥምቀታችን ጊዜ፡ በየአንገታችን ሊታሠርልን የሚያስፈልገው፡ በኖኅ አማካይነት፡ ከእግዚአብሔር፡ በቃል ኪዳን የተቀበልነውና የሰንደቅ ዓላማችንን ቀለማትን አዋሕዶ የያዘው፡ አረንጓዴ፥ ብጫና ቀይ ክር ማተብ ሊኾን ይገባል። ዳሩ ግን፡ ግብፃውያን፡ ያን፡ መለኮታዊ ሕያው ቅርሳችንን፡በእነርሱ፡ የባዕድ አምልኮ አረማዊነት ምልክታቸው ለውጠውት ይገኛል፤ ይኸውም፡እነርሱ፡ እስከዛሬ እየሠሩበት ባለውና ነጭ፥ ጥቁርና ቀይ በኾነው፡ በግብፃውያን ብሔራዊ ሰንደቅ ዓላማቸው ቀለማት መተካታቸው ነው።

ወደ ተደጋጋሚ ጥያቄዎች መመለሻ / Back to Frequently Asked Question

፩ኛ. የ ”ግእዝ” የጥሬ ዘሩ ቃል ትርጉም፡ “መጀመሪያ”, “ነፃ” እና “የጥንት ተፈጥሮ ጠባይ ወይም ባህሪይ” ማለት መኾኑ

፪ኛ. የእያንዳንዱ ፊደል የመጀመሪያ ቅርጽ አፍ ሳያስከፍት በድን በኾነው በተፈጥሮ ድምፅ ብቻ የሚነገር መኾኑ

፫ኛ. የፊደሉ መነሻ “አ” “አዳም” በሚል ቃል በወንድና ሴት ጾታ ለተፈጠሩት ለመጀመሪያዎቹ ሰዎች መጠሪያ መኾኑ

፬ኛ. በሰባት ብዛት የሚወሰን ቁጥር፤ የመለኮታዊ ሥራ ምሥጢር እንዳለበት ስለሚታመን፤ እያንዳንዱ ፊደል፤ በሰባት ስሞች ድምጾችና መልኮች ተለይቶ የሚታወቅና የሚነገር መኾኑ

፭ኛ. ሌሎቹ የሰዎች ቋንቋዎችና ፊደሎቻቸው በተናጋሪዎቻቸው ሕዝቦች ወይም ጎሣዎች ስም ለምሳሌ፤ ዐማርኛ፤ በዐምሓሮች፤ ዕብራይስጥ በዕብራዊያን፤ ዐረብኛ በዓረቦች ስም ሲጠሩ “ግዕዝ” ግን በራሱ ብቻ የሚጠራ መኾኑ

ወደ ተደጋጋሚ ጥያቄዎች መመለሻ / Back to Frequently Asked Question

፩. ዕለት (ቀን) የሚቀየረው፡ ከእኩለ ሌሊት፥ ማለትም፡ ከጨለማው ፮ኛ (ስድስተኛ)፥ ወይም፡ ከዕለቲቷ ፳፬ኛ (ሃያ አራተኛ) ሰዓት በኋላ ባለችው ቅጽበት ነው፤ ምክንያቱም፡ መሬት፡ በፀሓይ ዙርያ የምታደርገው፡ የ፩ (አንድ) ዕለት፥ ማለትም፡ የ፳፬ (ሃያ አራት) ሰዓታት፥ ወይም፡ የ፷ (ስድሳ) ኬክሮስ ዑደት አብቅቶ፡ የአዲሱ ዕለት ዑደት፡ ፩ ኬክሮስ፥ ወይም፡ ፩ ሰዓት ተብሎ የሚጀመርበት፡ የጊዜ ቀመር (አቈጣጠር) መነሻ፡ በዚያች በእኩለ ሌሊቷ አፍታ ላይ ስለኾነ ነው።

እኩለ ሌሊት፥ ማለትም፡ የጨለማው ጊዜ ፮ኛ፥ ወይም፡ የዕለቱ፡ ፳፬ኛ ሰዓት፡ ከዑደቱ ኺደት ዓናት፥ ወይም ቍንጮ፥ ወይም፡ ጫፍ ከደረሰ በኋላ፡ "ውድቅት" የተባለውን፡ የማዘቅዘቅ ርደቱን ወጥኖ፡ የንጋት ፍንጭ የኾነው የጎህ መቅደድና የፀሓይ ብርሃን ውጋጋን፡ የመፈንጠቁ ነፀብራቅ፡ በስተምሥራቁ አድማስ በኩል መታየቱ የሚጀመርበት አፍታ ነው።

ወደ ተደጋጋሚ ጥያቄዎች መመለሻ / Back to Frequently Asked Question

፳፪ቱ ቅዳሚዎችና መደበኞች ሆህያት፡ ለየቅላቸው፡ በዚያው በግእዝ ባሕርያቸው፡ ስመ አምላክነት ያለው ምሥጢራዊ ትርጓሜ አላቸው። ይኸውም እንደሚከተለው ነው፦

አ፡ አሌፍ ይባላል። በግእዙ፡ አሌፍ ብሂል፡ አብ ፈጣሬ ኲሉ ዓልም ይሚለው ትርጉሙ፡ አሌፍ፡ ዓለሙን ኹሉ የፈጠረ፡ እግዚአብሔር አብ ማለት ነው።

በ፡ ቤት ይባላል። በግእዙ፡ ቤት ብሂል፡ ባዕል እግዚአብሔር የሚለው፡ ቤት፡ እግዚአብሔር፡ ኹሉን የሚሰጥ ባለጸጋ ማለት ነው።

ገ፡ ጋሜል ይባላል። በግእዙ፡ ጋሜል ብሂል፡ ግሩም እግዚአብሔር የሚለው፡ ጋሜል፡ እግዚአብሔር የሚያስፈራ አምላክ ማለት ነው።

ደ፡ ዳሌጥ ይባላል። በግእዙ ዳሌጥ ብሂል ድልው እግዚአብሔር የሚለው፡ ዳሌጥ፡ እግዚአብሔር፡ በኹሉ ዝግጁ ማለት ነው።

ሀ፡ ሄ ይባላል። በግእዙ፡ ሄ ብሂል፡ ህልው እግዚአብሔር የሚለው ሄ እግዚአብሔር፡ በኹሉ አድሮ የሚኖር ማለት ነው።

ወደ ተደጋጋሚ ጥያቄዎች መመለሻ / Back to Frequently Asked Question

ልኡል እግዚአብሔር፡ በመልኩ በፈጠረው ሰብኣዊ ፍጡሩ ልቦና ውስጥ፡ ያሳደረው፡ ፍጹም እግዚአብሔራዊ እውቀትና በልቡ ጽላት ላይ ጽፎ ያስተማረው፡ ፍጹም እግዚአብሔራዊ ትምህርት አለ። ይኽ እውቀትና ትምህርት፡ በስነፍጥረታዊው የመለኮት ጥበብ፡ የተፈጸመ ትንግርትና በአምላካዊ ቸርነት የተደረገ የቃል ኪዳን ፍሬ ነው። ከዚኽ እውቀትና ትምህርት የሚበልጥ፡ የፍጡር እውቀትና ትምህርት ከቶ የለም። የዚኽ ተፈጥሮዋዊ ጸጋና ዘለአለማዊ በረከት፡ ተቀባይና ባለቤት ከኾነው ከራሱ ከእያንዳንዱ ሰው በኩል፡ ቢዘኽ ረገድ የሚጠበቅና የሚፈለግ በነፍስ ወከፍም ሊፈጸም የሚገባ፡ አንድ ብቸኛ የግዴታ ድርሻ አለ። ይኽም፡ ከፈጣሪው በልግስና የተሰጠውን ይኽንንው የልዕልና ዘውድ፡ በብቅዓት መቀዳጀትና ባህሪው የኾነውን የዚኽን ብልጽግና ተክል ኮትኩቶ ማሳደግ፡ ለበጎ ጥቅምም ማዋል ነው።

ይኽን እውነታ፡ ቸሩ እግዚአብሔር፡ አስቀድሞ በዘመነ ብሉይ በነብያት ባወጀው፡ እንዲኽ በሚለው ቃሉ ገሃድና እውን አድርጎታል።

ወደ ተደጋጋሚ ጥያቄዎች መመለሻ / Back to Frequently Asked Question

Pages